ማቴ 15:1-9 (አማ54)
“በዚያን ጊዜ ጻፎችና ፈሪሳውያን ከኢየሩሳሌም ወደ ኢየሱስ ቀረቡና፦ ደቀ መዛሙርትህ ስለ ምን የሽማግሎችን ወግ ይተላለፋሉ? እንጀራ ሲበሉ እጃቸውን አይታጠቡምና አሉት። እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ እናንተስ ስለ ወጋችሁ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ስለ ምን ትተላለፋላችሁ? እግዚአብሔር፦ አባትህንና እናትህን አክብር፤ ደግሞ፦ አባቱን ወይም እናቱን የሰደበ ፈጽሞ ይሙት ብሎአልና፤ እናንተ ግን፦ አባቱን ወይም እናቱን፦ ከእኔ የምትጠቀምበት መባ ነው የሚል ሁሉ፥ አባቱን ወይም እናቱን አያከብርም ትላላችሁ፤ ስለ ወጋችሁም የእግዚአብሔርን ቃል ሻራችሁ። እናንተ ግብዞች፥ ኢሳይያስ ስለ እናንተ፦ ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል፥ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤ የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል ብሎ በእውነት ትንቢት ተናገረ።”
Matthew 15:1-9 (ESV)
“Then Pharisees and scribes came to Jesus from Jerusalem and said, “Why do your disciples break the tradition of the elders? For they do not wash their hands when they eat.” He answered them, “And why do you break the commandment of God for the sake of your tradition? For God commanded, ‘Honor your father and your mother,’ and, ‘Whoever reviles father or mother must surely die.’ But you say, ‘If anyone tells his father or his mother, “What you would have gained from me is given to God,” he need not honor his father.’ So for the sake of your tradition you have made void the word of God. You hypocrites! Well did Isaiah prophesy of you, when he said: “‘This people honors me with their lips, but their heart is far from me; in vain do they worship me, teaching as doctrines the commandments of men.’””