ትምህርተ መንፈስ ቅዱስ
የጸጋ ስጦታዎች (ክፍል 2)
📌 በዚህ ትምህርት የጸጋ ስጦታዎችን በ2 እንከፍላቸዋለን
- 1️⃣ መንፈስ ቅዱስ ለእያንዳንዱ አማኝ የሚሠጣቸው (1ቆሮ12-14) ብቃቶች፣ ስራዎች ናቸው
- 2️⃣ የክርስቶስ ስጦታዎች ናቸው (ኤፌ 4:11) ሰዎች ናቸው
📌 በዚህ ሳምንት የመጀመሪያውን እንመልከት
- የጸጋ ስጦታን በተመለከተ ሰጪው አምላክ ፍጹም ነው።
- እግዚአብሔር የተሳሳተ ስጦታን አይሰጥም። ሰጪው ፍጹም ስለሆነ ስጦታዎቹም ፍጹማን ናቸው። ሰጪው ስህተት የለውም፤ ተቀባዩ ግን ፍጹም አይደለም።
- ፍጸም ስጦታዎች ፍጹማን ባልሆኑ እቃዎች/ተቀባዮች ማለት ነው።
- ፍጹም የሆኑ ስጦታዎች በደካማ እጆች ውስጥ ስለሚሆኑ አንዳንዴ ለተለየ አላማ ጥቅም ላይ ይውላሉ። ራስን ለማሳየት፣ ለንግድ ጥቅም ላይ ይውላሉ። በዚህ የተነሳ በጣም ብዙ ትርምስ አለ።
- ሁለት ቃላትን እንመልከት
📌 አቅላይነት እና አጥላይነት
● አቅላይ
- አንዳንድ ሰዎች እነዚህ ፍጹማን የሆኑ ስጦታዎች ፍጹማን ባልሆኑ ሰዎች ውስጥ ሲያዩ አቅላይ ይሆናሉ፣ የጸጋን ነገር ያቃልላሉ፣ ያክፋፋሉ፣ ቸል ይላሉ፣ አይጠሙም።
- እግዚአብሔር የጸጋ ስጦታን የምር እንድንይዝ ይፈልጋል።
- የጸጋ ስጦታ ትርፍ ትምህርት አይደለም፣ ጊዜ ከተረፈን የምናሰላስለው አይደለም። በጣም ልንጠማው የሚገባ ነው። ምክንያቱም ደግሞ ጌታን ተቀብለን ስንኖር እግዚአብሔር በጸጋ ስጦታ ጡንቻችንን ካላዳበረው እንዴት እንጨርሳለን? ከዘላለም ሕይወት መነጣጠል የለብንም።
- እርግጥ ሰው የሚድነው በጸጋ ስጦታ አይደለም፣ ሰው ትንቢት ስለተናገረ ወይ ስለፈወሰ አይጸድቅም (ማቴ 7)
- ትንቢት የተናገረ፣ ጋኔን ያወጣ ሁሉ መንግሥተ ሰማይ ይገባል ማለት አይደለም። ያ ማለት ግን አያስፈልግም ማለት አይደለም።
- በጸጋ ያዳነን አምላክ በጸጋ ይደግፈንና በጸጋ ያቆመንና ያጸድቀናል።
- በጸጋ ስጦታ ዙሪያ ስህተትም፣ ማሾፍም ስለበዛ፣ ሰውም ስላቀለለው እንዳይቀልብን! እግዚአብሔር ያከበደው ነውና እንጠንቀቅ።
- 📖 1ተሰ 5:19
- በጸጋ ስጦታ እያሾፍን እየዋልን በጸጋ ስጦታ የማገልገልን መታጠቅ እንታጠቃለን ብሎ ማሰብ አይቻልም። መቃወም አንድ ነው፤ ማሾፍ ሌላ ነገር ነው (ማቴ 12)።
- ጸጋን ከሚያክፋፋ ጋራ ኀብረት አይኑራችሁ። ስናክፋፋ ውለን፣ ስናክፋፋ አድረን በጸጋ እንድንሞላ መጠበቅ አንችልም፤ ያራከስነውን አይሰጠንም።
● አጥላይ
- የጸጋ ስጦታን ሁሉን የመቀበል ግዴታ የለብንም። ሰው በስሜቱም ብዙ ነገር ሊያደርግ ይችላል፤ ሰይጣንም አለ። ምክንያቱም ሰይጣን የጽድቅ አገልጋዮችን የመምሰል፣ የብርሀን መልአክ የመምሠል፣ ድንቅና ተአምራትን የማድረግ ችሎታ አለው።
- 📖 1ተሰ 5:19-21….አታጥፉ..ሁሉን ፈትኑ መልካሙን ያዙ
- የመንፈስ ቅዱስ ስራ በእግዚአብሔር ቃል የሚፈተሽ ነው፣ የሚመዘን ነው።
- ስለዚህ የማያቃልል ግን የሚያጠል መሆን አለብን።
- 📖 1ዮሐ 4:1
● ከማቅለልም ከማጥለልም በላይ መጠማት!
- ማቅለልና ማጥለል መታዘብ ናቸው፤ ታዛቢ ግን እንድንሆን አልተጠራንም፤ የምንጠማ እንድንሆን ያስፈልገናል።
- 📖 1ቆሮ 14:1
- እግዚአብሔር ከአቅማችንና ከችሎታችን በላይ በጸጋ ስጦታዎች እንዲጠቀምብን መራብ፣ ያስፈልገናል።
- የጸጋ ስጦታዎች ያሳድጋሉ፣ ያበስላሉ፣ ያንጻሉ።
- በጣም ብዙዎቻችን ያለመብሰላችን ምክንያት ያለማገልገላችን ነው። ምክንያቱም የሚንቀሳቀስ ነገር ነው የሚያድገው፣ ቁጭ ያለ ነገር አያድግም።
- በጸጋ ስጦታ ማገልገል ያንጸናል፣ ያነሳሳናል (ኤፌ 4:7)። ሁላችን አገልጋዮች ነን። ቤተክርስቲያን ሙሉ ናት። ምዕመኖቿ በጸጋ የታጠቁ ናቸው፤ መሪዎቿና አገልጋዮቿ ደግሞ አስታጣቂ ባለጸጋዎች ናቸው።
- 📖 ኤፌ 4:12-13 …ሙሉ ሰው ወደመሆን…ፍጹማን እስክንሆን ዘንድ..
● የጸጋ ስጦታዎችን ዝርዝር (ብቃቶችን) በጥቂቱ እንመልከት
➥ የማይመስሉቱ:- የጸጋ ስጦታ መሆናቸውን የማናስተውላቸው፣ የማንጸልይባቸው
- 📖 ሮሜ 12 …ማገልገል …
- መምከር
- ማገልገል
- መለገስ
- ማስተዳደር
- ምህረት ማድረግ
- የጸጋ ስጦታን የምንጠማው ለመድረክ አይሁን። መድረክ ላይ ያሉት የአካል ብልቶች በጣም ጥቂት ናቸው። ከመድረክ ጀርባ ያሉት ሲገለጡ ፊት ካሉት ይበልጣሉ።
- የምናዳምቀውና የምንጸልየውም በመድረክ ላይ ላሉት ነው።
- ቤተክርስቲያን መታመም የለባትም በጀርባ/በውስጥ ያሉትን ለማየት።
- እግዚአብሔር ምን መክሊት ሰጥቶናል? ነው እንጂ ያልሆነውን እንድሆን እግዚአብሔር አልጠራንም። እግዚአብሔር የሚጠይቀን ለሰጠን ነገር ብቻ ነው።
- በተሰጠን ማገልገል ትህትናን ይጠይቃል።
➥ ተአምራዊ የሆኑ (1ቆሮ 12 ያሉት ዘጠኙ)
- በሶስት እንከፍላቸዋለን
1) የንግግር ስጦታዎች
- ልሳን መናገር
- በልሳን የተነገረውን መተርጎም
- ትንቢት መናገር
2) የሀይል ስጦታዎች
- ፈውስ
- ተአምራትን ማድረግ
- እምነት
3) የመገለጥ ስጦታዎች
- ጥበብን መናገር
- እውቀት መናገር
- መናፍስትን መለየት
📌 የንግግር ስጦታዎች
- የተለመዱ የስጦታ አይነቶች ናቸው
- ለእያንዳንዳችን የሚሰጡ ስጦታዎች ናቸው
- በጉባዬ ውስጥ የሚገለጡ ናቸው
● በልሳን የመናገር ስጦታ
- ተናጋሪው በማያውቀው ቋንቋ የመናገር ብቃት ማለት ነው።
- 📖 ሐዋ ስራ 2:
- ልሳን መናገርን ድንቅ ያደረገው ያልተማሩ ሰዎች መናገራቸው ነው።
- በዚህ ዘመን በልሳን የመናገር ስጦታ ይኑር አይኑር የሚያጠራጥረው ሁላችን በልሳን ስለምንናገር ነው።
- በልሳን መናገር ለማያምኑ ምልከት ይሆናል (1ቆሮ 14:22)። ተናጋሪውን ያንጻል፣ በጉባኤ ሲተረጎም ደግሞ ጉባኤን ያንጻል 1ቆሮ 14:4)
- በልሳን መጸለይ ከአይምሯችን ያወጣናል፣ ከምናውቀው ከውስን ቋንቋ ያወጣናል። ያላሰብነውን ያጸልየናል (1ቆሮ14:14-15)።
● በልሳን የተነገረውን የመተርጎም ስጦታ
- ተአምር የሚያደርገው ነገር ተርጓሚውም አለማወቁ ነው
- ልሳን የማይተረጎም ከሆነ ለእግዚአብሔር ነው የሚነገረው።
- 📖 1ቆሮ 14:5፣ 13
- በልሳን ለመናገር እንደምንጠማ ለመተርጎምም እንጠማ።
● ትንቢት መናገር
- ትንቢት መናገር ማለት ነቢይ መሆን ማለት አይደለም።
- ትንቢት ለእግዚአብሔር ልጆች በሙሉ የተሰጠ ነው።
- ትንቢት እግዚአብሔርን ወክሎ መናገርና መስማት ማለት ነው።
- ከእግዚአብሔር መስማት ደግሞ ለሁሉም የተሰጠ ነው። እግዚአብሔር የተናገረንን ለማጽናት ትንቢትን ያመጣል።
- ሁላችን ሰሚዎች እንድንሆን የእግዚአብሔር ልጆች እንድንሆን፣ በመንፈስ እንድንጸልይ ተጠርተናል።
- የትንቢት አላማ ሁልጊዜ የወደፊቱን መናገር አይደለም።
- 📖 1ቆሮ 14:3 ያንጻል፣ ይመክራል፣ ያጽናናል
📌 የጸጋ ስጦታ ፍላጎት ያብዛልን!
- በጸጋ ስጦታ የማገልገል እውነትና ድፍረት ተሰጥቶናል።
- በጸጋ ስጦታ ለማገልገል አንድ ቀን ፍጹማን እስክትሆኑ አትጠብቁ።
- 📖 1ጢሞ4:14 ማነሳሳት ይጠይቃል
- ምንድነው የተሰጣችሁ የጸጋ ስጦታ? እሱን ለማወቅ እንጸልይ።