የማቴዎስ ወንጌል 9:1-8 (አማ54)
በታንኳም ገብቶ ተሻገረና ወደ ገዛ ከተማው መጣ።እነሆም፥ በአልጋ የተኛ ሽባ ወደ እርሱ አመጡ። ኢየሱስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን፡— አንተ ልጅ፥ አይዞህ፥ ኃጢአትህ ተሰረየችልህ፡ አለው። እነሆም፥ ከጻፎቹ አንዳንዱ በልባቸው፡— ይህስ ይሳደባል፡ አሉ። ኢየሱስም አሳባቸውን አውቆ እንዲህ አለ፡— ስለ ምን በልባችሁ ክፉ ታስባላችሁ? ኃጢአትህ ተሰረየችልህ ከማለት ወይስ፡— ተነሣና ሂድ፡ ከማለት ማናቸው ይቀላል? ነገር ግን በምድር ላይ ኃጢአትን ያስተሰርይ ዘንድ ለሰው ልጅ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ፥ በዚያን ጊዜ ሽባውን፡— ተነሣ፤ አልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ፡ አለው።ተነሥቶም ወደ ቤቱ ሄደ። ሕዝቡም አይተው ተደነቁ፥ ለሰውም እንዲህ ያለ ሥልጣን የሰጠ እግዚአብሔርን አከበሩ።
Matthew 9:1-8 (ESV)
And getting into a boat he crossed over and came to his own city.And behold, some people brought to him a paralytic, lying on a bed. And when Jesus saw their faith, he said to the paralytic, “Take heart, my son; your sins are forgiven.” And behold, some of the scribes said to themselves, “This man is blaspheming.” But Jesus, knowing their thoughts, said, “Why do you think evil in your hearts? For which is easier, to say, ‘Your sins are forgiven,’ or to say, ‘Rise and walk’? But that you may know that the Son of Man has authority on earth to forgive sins”—he then said to the paralytic—“Rise, pick up your bed and go home.” And he rose and went home. When the crowds saw it, they were afraid, and they glorified God, who had given such authority to men.